በግደይ ገብረኪዳን
የ2012 ኦሎምፒክ መክፈቻና መዝጊያ ስነ ስረአት በአምስቱም ክፍለ ዓለማት አንድ ቢሊዮን ገደማ ሰዎች ለመታየት በቅቷል፡፡ ሁሌም ከፍተኛ ቦታ እንደሚሰጣቸው የሚድያ ክስተቶች ሁሉ የዓለማችን ቁንጮዎች መልእክቶች፣ ምልክቶች እና አጀንዳዎቻቸው የትእይንቱ አካል ነበሩ፡፡ እኚህን በለንደን ኦሎምፒክ እንዳስሳለን፡፡
የኦሎምፒክ ክብረ በዓላት በምድራችን ሰፊ ተመልካች ከሚያገኙት ትእይንቶች አንዱ ነው፡፡ ላስተናጋጅ ሃገሪቱ ታላቅነቷን የምታሳይበት አጋጣሚዋ ነው፡፡ (ወጪውን በግብር መልክ የሚሸፍነው ድሃው ህብረተሰብ ይሸከመዋል፡፡) የለንደን ኦሎምፒክም ከዚሁ የተለየ አልነበረም፡ የእንግሊዝ ታሪክ፣ ባህል፣ እና ስኬቶች በበዓሉ ቀርበው በሚገባ ተሞግሰዋል፡፡ አንዳንድ ክስተቶች እፁብ ነበሩ ሌሎች የሚያስቁም ነበሩ፤ የሚያስፈሩ እና የሚረብሹም ክስተቶች ነበሩ፡፡ አንዳንዶቹ ከፍተኛ ተምሳሌትነት ያላቸውና የቁንጮዎቹን አጀንዳ የሚያንፀባርቁ ነበሩ፡፡ ለንደን የዓለማችን ቁንጮ የስልጣን ማማዎች መገኛ እንደመሆኗ በበዓላቱ የቁንጮዎቹ ምልክቶችና ፍልስፍና ባይንፀባረቅ ኑሮ ይበልጡኑ አስገራሚ ይሆን ነበር፡፡
ሁሉም ነገር ተምሳሌታዊ ነበር ማለት አይደለም፣ ሁሉም ምልእክትም አይን ያወጣ ግልፅነት አልነበረውም፣ በዓሉ በፈጀበት ሰዓቶች ግን ለመላው ዓለም ህዝብ ሰፊ መልእክት ተላልፏል፡፡ እስኪ እንመልከታቸው፡፡ Read the rest of this entry »